| | ሰቆ 3:38 ክፉም ሆነ መልካም ነገር፣ ከልዑል አፍ የሚወጣ አይደለምን? ❒️ |
| | ኢዮ 38:7 ይህም የሆነው የንጋት ከዋክብት በዘመሩበት ጊዜ፣ መላእክትም[78] እልል ባሉበት ጊዜ ነበር። ❒️ |
| | 1ጢሞ 4:4 እግዚአብሔር የፈጠረው ማንኛውም ነገር መልካም ነውና፤ በምስጋና ከተቀበሉትም የሚጣል ምንም ነገር የለም፣ ❒️ |
| | መዝ 19:1-2 ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፤ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያውጃሉ። ቀን ለሌላው ቀን ይናገራል፤ ሌሊትም ለሌሊት ዕውቀትን ይገልጣል፤ ❒️ |
| | ዘፍ 2:2 እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ይሠራ የነበረውን ሥራ በሰባተኛው ቀን ላይ ፈጽሞ ነበር፤ ስለዚህ ከሠራው ሥራ ሁሉ በሰባተኛው ቀን ዐረፈ።[3] ❒️ |
| | ዘፀ 20:11 እግዚአብሔር (ያህዌ) ሰማይንና ምድርን፤ ባሕርንና በውስጡም ያሉትን ሁሉ በስድስት ቀን ፈጥሮ፤ በሰባተኛው ቀን አርፎአልና። ስለዚህ እግዚአብሔር (ያህዌ) የሰንበትን ቀን ባረከው፤ ቀደሰውም። ❒️ |
| | ዘፍ 1:8 እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ጠፈርን “ሰማይ” ብሎ ጠራው። መሸ፤ ነጋም፤ ሁለተኛ ቀን። ❒️ |
| | መዝ 104:31 የእግዚአብሔር ክብር ለዘላለም ጸንቶ ይኑር፤ እግዚአብሔር በሥራው ደስ ይበለው፤ ❒️ |
| | ዘፍ 1:13 መሸ፤ ነጋም፤ ሦስተኛ ቀን። ❒️ |
| | ዘፍ 1:19 መሸ፤ ነጋም፣ አራተኛ ቀን። ❒️ |
| | ዘፍ 1:23 መሸ፤ ነጋም፤ አምስተኛ ቀን። ❒️ |
| | መዝ 104:24 እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህ እንዴት ብዙ ነው! ሁሉን በጥበብ ሠራህ፤ ምድርም በፍጥረትህ ተሞላች። ❒️ |
| | ዘፍ 1:5 እግዚአብሔርም (ኤሎሂም) ብርሃኑን “ቀን”፣ ጨለማውን “ሌሊት” ብሎ ጠራው። መሸ፤ ነጋም፤ የመጀመሪያ ቀን። ❒️ |