| መዝ 95:5 እርሱ ፈጥሮአታልና፣ ባሕር የእርሱ ናት፤ እጁም የብስን አበጀ። |
| መዝ 24:1-2 የዳዊት መዝሙር ምድርና በእርሷ ያለው ሁሉ፣ ዓለምና በውስጧ የሚኖር ሁሉ የእግዚአብሔር ነው፤ እርሱ በባሕሮች ላይ መሥርቶአታልና፤ በውሆችም ላይ አጽንቶአታል። |
| መዝ 33:7 የባሕርን ውሃ በአንድ ዕቃ ይሰበስባል፤[49] ቀላዩንም በአንድ ስፍራ ያከማቻል። |
| 2ጴጥ 3:5 ነገር ግን እነዚህ ሰዎች ሰማያት ከጥንት ጀምሮ በእግዚአብሔር ቃል ተፈጥረው እንደሚኖሩ፣ መሬትም በውሃ መካከልና በውሃም እንደ ተሠራች ሆን ብለው ይክዳሉ፤ |
| መክ 1:7 ወንዞች ሁሉ ወደ ባሕር ይፈሳሉ፤ ባሕሩ ግን ፈጽሞ አይሞላም፤ ወንዞች ወደ መጡበት ስፍራ፣ ወደዚያ እንደ ገና ይመለሳሉ። |
| ምሳ 8:28-29 ደመናትን በላይ ባጸና ጊዜ፣ የውቅያኖስን ምንጮች በመሠረተ ጊዜ፣ ለባሕር ድንበርን በከለለ ጊዜ፣ ውሆችም የእርሱን ትእዛዝ እንዳያልፉ፣ የምድርንም መሠረቶች ወሰን ባበጀ ጊዜ፣ |
| ኢዮ 38:8-11 “ባሕር ከማሕፀን በወጣ ጊዜ፣ በር የዘጋበት ማን ነው? ደመናውን ልብሱ፣ ጨለማንም መጠቅለያው አደረግሁለት፣ ድንበር ወሰንሁለት፤ መዝጊያና መወርወሪያውን አበጀሁለት። ‘እስከዚህ ድረስ ትመጣለህ፤ ማለፍ ግን አትችልም፤ የዕቡይ ማዕበልህም ገደብ ይህ ነው’ አልሁት። |
| መዝ 136:5-6 ሰማያትን በብልኀት የሠራ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤ ምድርን በውሃ ላይ የዘረጋ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና። |
| ኤር 5:22 ልትፈሩኝ አይገባችሁምን?” ይላል እግዚአብሔር፤ “በእኔ ፊት ልትንቀጠቀጡስ አይገባምን? ለዘላለም ዐልፎት መሄድ እንዳይችል፣ አሸዋን ለባሕር ድንበር አደረግሁ፤ ማዕበሉ እየጋለበ ቢመጣ ከዚያ አያልፍም፤ ሞገዱ ቢጮኽም ሊያቋርጠው አይችልም። |
| መዝ 104:3 የእልፍኝህን አግዳሚ በውሆች ላይ አኖርህ፤ ደመናትን ሠረገላህ አደረግህ፤ በነፋስ ክንፍ ትሄዳለህ። |
| ኢዮ 26:10 ለብርሃንና ለጨለማ ድንበር ይሆን ዘንድ፣ በውሆች ላይ የአድማስ ክበብ አበጀ። |
| መዝ 104:5-9 ለዘላለም እንዳትናወጥ፣ ምድርን በመሠረቷ ላይ አጸናሃት። በጥልቁ እንደ ልብስ ሸፈንሃት፤ ውሆችም ከተራሮች በላይ ቆሙ። በገሠጽሃቸው ጊዜ ግን ፈጥነው ሄዱ፤ የነጐድጓድህንም ድምፅ በሰሙ ጊዜ ሸሹ። በተራሮች ላይ ፈሰሱ፤ ወዳዘጋጀህላቸው ስፍራ፣ ወደ ሸለቆዎች ወረዱ። ተመልሰው ምድርን እንዳይሸፍኑ፣ አልፈውም እንዳይመጡ ድንበር አበጀህላቸው። |
| ራእ 10:6 እርሱም ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚኖረው፣ ሰማይንና በውስጡ ያሉትን፣ ምድርንና በውስጧ ያሉትን፣ ባሕርንና በውስጡ ያሉትን በፈጠረው በእርሱ ማለ፤ እንዲህም አለ፤ “ከእንግዲህ መዘግየት አይኖርም፤ |
| ዮና 1:9 እርሱም፣ “እኔ ዕብራዊ ነኝ፤ የብስንና ባሕርን የፈጠረውን፣ የሰማይን አምላክ እግዚአብሔርን አመልካለሁ” አለ። |
| ኢዮ 26:7 የሰሜንን ሰማይ በሕዋው ላይ ዘረጋው፤ ምድርንም እንዲያው በባዶው ላይ አንጠለጠላት። |