Use Secondary Monitor    Cross Reference    Verses by Topic        Show Version:       

Selected Lyrics   Member Access

  Blank Screen    Lines per Slide:     Font Size:       Show Window as Tab          🖶       Alignments:  
   የተፈታው እስራቴ --- አዜብ ሀይሉ
Background
Videos
Background
Images
Text Colors
 1  (የታሰረችው ውርንጭ ለኢየሱስ መቀመጫ
ታስፈልገዋለችና አምጧት በፍጥነት (በቶሎ) ፍቱና) (2X)
(ለምን ቢባል ሊከብርባት ለምን ቢባል ሊነግስባት
እራሱን በላይዋ አድርጐ ኢየሩሳሌም ሊገባባት (ሊጓዝባት)) (2X)
 2  የተፈታው እስራቴ የታወጀው አርነቴ
በቀራንዮ በጐልጐታ እራሱን ሲሰጥ ለእኔ ጌታ
ተፈጸመ ሲል ሲናገር የተጫነኝ ክፉ ቀንበር
ሲወድቅ አየሁ ሲሰባበር ይሁን ለእርሱ ብዙ ክብር
 3  በድቅድቁ ጨለማ ተጥዬ ስደናበር
በጠበቀው ሰንሰለት ባማይፈታው እስር
እንድጠፋ ለሲዖል የታጨሁ በመሆኔ
በግፍ ነፍሴ ሊሰዋ ሊታረድ በጭካኔ
አዋጅ ወጣ ከሰማይ ከዙፋን ከመቅደሱ
ፍቷትና ትለቀቅ ተባለ ክብር ለእርሱ
አገኛታለሁ ብሎ የጐመጀው ጠላቴ
እፍረት ተከናነበ እኔም ጸና ጉልበቴ
 4  የተፈታው እስራቴ የታወጀው አርነቴ
በቀራንዮ በጐልጐታ እራሱን ሲሰጥ ለእኔ ጌታ
ተፈጸመ ሲል ሲናገር የተጫነኝ ክፉ ቀንበር
ሲወድቅ አየሁ ሲሰባበር ይሁን ለእርሱ ብዙ ክብር
 5  አጥምዶብኝ ወጥመዱን እግሮቼ ስር ዘርግቶ
መረብ ውስጥ እንድገባ ፈልጐ እጅግ ጓጉቶ
መስሎት የተሳካለት የገባሁ በመዳፉ
ደስ ብሎት ጨፈረ ሊውጠኝ ይዞ በአፉ
የይሁዳው አንበሳ የቀራንዮ ጀግና
ጉልበተኛው ኢየሱስ ስመጥሩ ገናና
ፍፁም አይሆንም ብሎ ከሰማያት ወረደ
እራሱን ስለእኔ ሲሰጥ ጠላቴ ተዋረደ
 6  የተፈታው እስራቴ የታወጀው አርነቴ
በቀራንዮ በጐልጐታ እራሱን ሲሰጥ ለእኔ ጌታ
ተፈጸመ ሲል ሲናገር የተጫነኝ ክፉ ቀንበር
ሲወድቅ አየሁ ሲሰባበር ይሁን ለእርሱ ብዙ ክብር
 7  ወገኖች የምስራች ተሸንፏል ዲያቢሎስ
የሞትን ጣር ባጠፋው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ
ከመስቀሉ ስር ያኔ አድቅቆታል ቀጥቅጦ
ለሚያምኑበት በሙሉ አስገዝቶታል ረግጦ
ወጥመዱ ተሰበረ ነፍሴ እንደወፍ በረረች
ሰይጣን ባዶ እጁን ቀረ ከግዞቱ አመለጠች
ሞትስ መውጊያው የታለ ጌታ ሞቶ ተነሳ
ከሲዖል ምርኮን ማርኮ በስልጣኑ ድል ነሳ
 8  የተፈታው እስራቴ የታወጀው አርነቴ
በቀራንዮ በጐልጐታ እራሱን ሲሰጥ ለእኔ ጌታ
ተፈጸመ ሲል ሲናገር የተጫነኝ ክፉ ቀንበር
ሲወድቅ አየሁ ሲሰባበር ይሁን ለእርሱ ብዙ ክብር (2X)
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
  
Yellow
White
Gold
Silver
Gray
Red
Maroon
Olive
Lime
Green
Aqua
Teal
Blue
Navy
Brown
Purple
Magenta
Orange
Cyan

 Go Back